ሐሙስ 20 ጁን 2019

ጾመ ሐዋርያት


ጾመ ሐዋርያት




በየአመቱ በዕለተ ሰኑይ ብቻ (ሰኞ ቀን ብቻ)የሚጀምሩ ሦስት አጽዋማት አሉ።እነርሱም ዓቢይጾም፣ ጾመ ነነዌ እና ጾመ ሐዋርያት ናቸው። እነዚህአጽዋማት ምን ጊዜም ቅበላቸው እሁድ ሲሆንየሚገቡት ደግሞ ሰኞ ቀን ነው።በየትኛውም አመትይህን ዕለት አይለቁም።ቤተ ክርስቲያናችንያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ውስጥበማስገባት፣ በየግላችንም ያጋጠሙንን መንፈሳዊናሥጋዊ ውጊያዎች በማሰብ ድል የምናደርግበትንኃይል ፈጣሪያችን ይሰጠን ጾሙን ከወትሮውበበለጠ ጥንቃቄ ልንጾመው ይገባናል፡፡
የጾሙን ታላቅነት ተረድተን እንድንጾመውየትመጣውን፣ ትንቢቱን፣ ምሳሌውንና ምሥጢሩንመረዳት አጋዥ ስለሚሆነን አስቀድመን ስለጾሙእንማር ዘንድ በአጭሩ አቅርቤዋለሁ! የምችለውንያህል እጽፍ ዘንድ ብርታቱንና ጥበቡን የሰጠኝአምላከ ቅዱሳን ሐዋርያት ክብር ምስጋናይድረሰው! አሜን!
ጾመ ሐዋርያት በራሳቸው በሐዋርያት የተጀመረ ጾምእንደመሆኑ መጠን በአንደኛው መቶ ክፍለ ዘመንማለትም ከዛሬ አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዓመታትበፊት ጀምሮ ሲጾም የኖረ ጾም ነው፡፡ ለዚህምየመጽሐፍ ቅዱስ፣ የአዋልድ መጻሕፍትና የታሪክበርካታ ምስክሮች አሉ፡፡ ስለዚህ ጾሙን እንደእንግዳ ነገር መቁጠርና ዘመን አመጣሽ አድርጎማየት የራስን አላዋቂነት ያሳያል፡፡ ይህን ማለትያስፈለገው ጥቂቶች ጾሙን ድሮ ያልነበረና ዘመንአመጣሽ አድርገው ስለሚናገሩ ነው፡፡
      ጾመ ሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን ዕድሜያቸውለጾም የደረሱ ምእመናን በሙሉ እንዲጾሙአቸውካወጀቻቸው ሰባት የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በጌታችንና በአምላካችንበኢየሱስ ክርስቶስ አንደበት ቀን የተቀጠረለት፣ትንቢት የተነገረለትና ምሳሌ የተመሰለለት ጾምመሆኑ ከአጽዋማት ሁሉ ለየት ያደርገዋል፡፡
  ጌታችን ስለዚህ ጾም ትንቢተ በመናገር፣ ምሳሌበመመሰል ሰፊ ትምህርት የሰጠው ፈሪሳውያን ወደእርሱ ቀርበው ‹‹ደቀ መዛሙርትህ የማይጦሙትስለ ምንድር ነው?›› ብለው በጠየቁት ጊዜ ነው፡፡እርሱም ሲመልስ እንዲህ አላቸው፡- ‹‹ሚዜዎችሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን? ነገርግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራትይመጣል፤ በዚያ ጊዜም ይጦማሉ፡፡ በአረጀ ልብስአዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤ መጣፊያው ልብሱንይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል፡፡ በአረጀአቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ቢደረግ ግን አቁማዳው ይፈነዳል፤ የወይን ጠጁምይፈሳል፡፡ አቁማዳውም ይጠፋል፡፡ ነገር ግን አዲሱንየወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል ሁለቱምይጠባበቃሉ፡፡›› (ማቴ9.14-17)
በመቀጠልእስከ መጨረሻ የምንመለከተው ከላይየሰፈረውን የማቴዎስ ወንጌል አጭር ገጸ ንባብሐሳብ በመሆኑ መለስ እያሉ ታሪኩን ማንበብወይም በልብ ከመዘገቡ በኋላ ቀጣዩን ክፍልማንበብ ምሥጢሩን ለመረዳት ያግዛል፡፡
      በዚህ የጌታችን መልስ ውስጥ ‹‹ነገር ግንሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣልበዚያ ጊዜም ይጦማሉ፡፡›› የሚል ስለ ጾመሐዋርያት የተነገረ የትንቢት ቃል እናገኛለን፡፡ ይህአምላካዊ ቃል ጾሙ ስለሚጀመርበት ወራት ቀጠሮይሰጣል፡፡ ያም ጊዜ ሙሽራው ከእነርሱ ከተወሰደበኋላ ያለው ጊዜ ነው፡፡ ‹‹ሙሽራው ከተወሰደ››በኋላ ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ካረገበኋላ ማለት ሲሆን በቤተ ክርስቲያን ጾመ ሐዋርያትከዕርገት በኋላ የሚጀምረው በዚህ ቃል ምክንያትነው፡፡ ይህም ቤተ ክርስቲያን ምን ያህል መጽሐፍቅዱሳዊ መሠረት ያላት መሆኗን ያሳያል፡፡
      ጾመ ሐዋርያት ከዕርገት በኋላ ለዐሥር ቀናትያህል ዘግይቶ እንጂ ወዲያው አይጀምርም፡፡ምክንያቱም የሐዋርያት ሰውነት በአዲስ ሁኔታጌታችን ላዘጋጀው የአዲስ ኪዳን ጾም ተመቻችቶያልተገኘ በመሆኑ ነው፡፡ ስለዚህ በመጀመሪያየሐዋርያት ሰውነት ለጾሙ መዘጋጀት ነበረበት፡፡ከዚያ በኋላ ሐዋርያት መጾም ጀምረዋል፡፡ ይህምበጌታችንን የመልስ ቃል ውስጥ የተካተተ እንጂየፈጠራ ድርሰት አይደለም፡፡ ‹‹በአረጀ ልብስ ላይ››እና ‹‹በአረጀ አቁማዳ›› የሚሉት ሁለት ተከታታይምሳሌያዊ ማብራሪያዎች ሐዋርያት ሰውነታቸውበመንፈስ ቅዱስ ከመታደሱ በፊት ጾም መጾምእንደማይጀምሩ ወይም እንደሌለባቸው የሚያስረዱምሳሌዎች ነበሩ፡፡ ስለዚህ ሐዋርያትየተዘጋጀላቸውን ጾም መጾም የጀመሩት ከኢየሱስክርስቶስ ዕርገት በኋላ በዐሥረኛው ቀን በወረደ ጸጋመንፈስ ቅዱስ የሕይወት ሕድሳት አግኝተው ነው፡፡
      ከላይ በተጠቀሰው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስትምህርት ውስጥ ስለ ጾመ ሐዋርያት የቀረቡ ሦስትዓይነት ምሳሌዎችን እናገኛለን፡፡ ምሳሌዎቹበምሥጢር የተሞሉ በርካታ መንፈሳዊመልእክቶችን ያዘሉ ናቸውና ተራ በተራእንመለከታቸዋለን፡፡
      1ኛ. ‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለሊያዝኑ ይችላሉን?›› የሚለው ዐረፍተ ነገር በገጸንባቡ ውስጥ ስለ ሐዋርያት ጾም የተመሰለውየመጀመሪያው ምሳሌ ነው፡፡ ሚዜዎች የተባሉትእንደ መጥምቁ ዮሐንስ መንገድ የሚጠርጉ፣የሚያስተምሩና ምእመናንን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስየሚያቀረቡ ሁሉ ናቸው፡፡ ሙሽሪትን ወደ ሙሽራውመውሰድ የሚዜዎች ሥራ መሆኑ በአይሁድናበኢትዮጵያውያን ባህል ሲሠራበት የኖረ ነው፡፡ስለዚህ ዋነኞቹ ሚዜዎች ሐዋርያት ናቸው ማለትነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሙሽራ ሲሆን ቤተክርስቲያን (ምእመናን) ደግሞ መርዓት (ሴትሙሽራ) ትባላለች፡፡ (2ቆሮ11.2፤ ዮሐ3.29)
‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑይችላሉን?›› ሲል ሚዜዎች ሙሽራውን ለማስደሰትሲሉ ምንም የሚያሳዝን ነገር ቢያጋጥማቸውምእንኳን ጨክነው በመቻል ያሳልፉታል እንጂበሙሽራው ፊት እንደማያዝኑ፤ እንደዚሁም መጾምተገቢ ነገር ቢሆንም ሐዋርያት ኢየሱስ ክርስቶስከእነርሱ ጋር ሳለ መጾም እንደማይገባቸው ነገር ግንከእነርሱ ተለይቶ ሲያርግ መጾም እንደሚጀምሩያስረዳል፡፡
በዚህ ምሳሌያዊ ንባብ ውስጥ ጾም በኀዘንተመስሏል፡፡ መጾም ተድላነቱ ለነፍስ እንጂ ለሥጋአይደለምና፡፡ ሥጋ ጾምን እስኪለምድ ድረስ ቅጣትይሆንበታል፡፡ ስለዚህ በጾም ነፍስ ስትደሰት ሥጋግን ያዝናል፡፡ በዚህ ምክንያት ጾም በኀዘንተመስሏል፡፡ በዚህም ምክንያት ጾም በብዙየመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ከኀዘን፣ ከዕንባ፣ ከጸጸትናከንስሐ ጋር ተያይዞ ቀርቧል፡፡ (ኢዩ2.12)
2ኛ. ‹‹በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱምየባሰ ይሆናል፡፡›› ይህ ዐረፍተ ነገር ደግሞሁለተኛው ምሳሌ ነው፡፡ እራፊ ማለት ቅዳጅ ወይምመጣፊያ ጨርቅ ማለት ነው፡፡ የስፌት ባለሙያ ባረጀልብስ ላይ አዲስ ጨርቅ አይጥፍም (አይሰፋም)ወይም አይለጥፍም፡፡ ይህም አንደኛ ግንጥል ጌጥእንዳይሆን፤ ሁለተኛ ላሮጌ ልብስ ሲባል አዲሱንማበላሸት እንዳይመጣና አዲሱ ካሮጌውስለሚበረታ የባሰ እንዳይቦጭቀው በማሰብ ነው፡፡
በምሳሌው መሠረት በጣፊ ወይም በልብስ ሰፊየተመሰለው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ በአዲስ እራፊጨርቅ ምሳሌነት የተወከለው ደግሞ ኢየሱስክርስቶስ በአዲስ ኪዳን እንድንጾመው የሠራልንጾም ነው፡፡ የተቀደደውና መጣፊያ የሚያስፈልገውልብስ ደግሞ የሐዋርያት ሕይወት ምሳሌ ነው፡፡
እንደ ምሳሌው ሁሉ ሰዎች የክርስቶስ ልብሶችይባላሉ፡፡ ‹‹አልባሲሁሰ ለክርስቶስ መሃይምናንእሙንቱ›› እንዲል፡፡ ይህም ‹‹የክርስቶስ ልብሶቹምእመናን ናቸው፡፡›› ማለት ነው፡፡ ክርስቶስምለሰዎች ልብሳቸው ነው፡፡ ሐዋርያው ‹‹እናንተየተጠመቃችሁ ክርስቶስን ለብሳችኋል›› ብሏልና፡፡(ገላ3.27) ምእመናን የክርስቶስ ልብሶች ናቸውማለት የክብሩ መገለጫዎች ናቸው ማለት ነው፡፡ልብስ የክብር መገለጫ ይሆናልና፡፡ እርሱ ደግሞለምእመናን ልብስ ነው ማለት ጌጣቸው፣ነውራቸውን የሚሸፍንላቸውና ክብራቸውም እርሱነው ማለት ነው፡፡
ጾም ‹‹እራፊ›› መባሏ ምሥጢር አለው፡፡ ይኸውምእራፊ የተለያየውን እንደሚያቀራርብና አንድእንደሚያደርግ ጾምም የተለያዩ ፈቃዳት ያሏቸውንነፍስና ሥጋ አንድ ታደርጋለች፡፡ ከዚህም በላይከእግዚአብሔር የተለየውን ሰውም አስታርቃ አንድታደርገዋለች፤ ከመንጋውም እንዲቀላቀልትረዳዋለች፡፡
‹‹በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱምየባሰ ይሆናል፡፡›› ማለት አንድ የስፌት ባለሙያ ባረጀልብስ ላይ አዲስ እራፊ እንደማይጥፍ ሁሉ ኢየሱስክርስቶስም የሐዋርያት ሰውነት በኃጢአት ያረጀ ሆኖሳለ በመንፈስ ቅዱስ ሳያድስላቸው አዲስ የሠራውንየአዲስ ኪዳን ጾም ጹሙ ብሎ ሐዋርያትንአያዛቸውም ማለት ነው፡፡ ሰውነታቸው ሲታደስ ያንጊዜ ግን ይጾማሉ፡፡     
ይህ አገላለጥ እግዚአብሔር መንጋዎቹን ያለአቅማቸው እንዲሸከሙ የማያደርግ አዛኝ ጌታመሆኑን ያሳያል፡፡ እንዴት ቢባል ሐዋርያትንሊፈጽሙት በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ እያሉእንዲጾሙ አላዘዛቸውምና፡፡ ፈጣሪ ለሕዝቡ መቼሕግ መስጠት እንዳለበት በሚገባ ያውቃል፡፡ለእስራኤላውያን በባርነት ሳሉ ዐሥርቱ ትእዛዛትንያልሰጣቸው ስለዚህ ነው፡፡ ቢሰጣቸውምሊጠብቁት አይችሉም ነበርና፡፡ በባርነት ያለ ሰውየራሱ ነጻነት እስከሌለው ድረስ የፈቀደውን ማድረግአይችልም፡፡ በታላላቅ ተአምራት ከባርነትካወጣቸው በኋላ ግን ሕጉን ሰጣቸው፡፡ ስለዚህከክርስቲያን ወገን ማንም ቢሆን ከአቅሙ በላይየሆነ ነገር ፈጣሪ እንዳዘዘው አያስብ፡፡ የታዘዝነውሁሉ በዐቅማችን ልክ እንደሆነ እንመን፡፡
3ኛ. ‹‹በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖርየለም፤ ቢደረግ ግን አቁማዳው ይፈነዳል: የወይንጠጁም ይፈሳል፡፡ አቁማዳውም ይጠፋል፡፡›› ይህስለ ጾመ ሐዋርያት የተመሰለው ሦስተኛውናየመጨረሻው ምሳሌ ነው፡፡
በአረጀ አቁማዳ የተመሰለው ሐዋርያት በጸጋመንፈስ ቅዱስ ሳይታደሱ በፊት የነበራቸው ሕይወትሲሆን፤ በአዲስ ወይን የተመሰለው ደግሞ ጌታችንበወንጌል የመሠረተልን ጾም ነው፡፡ የጾም ሕግንየሰጠን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ደግሞ በጠጅ ጣዩ(በጠማቂው) ተመስሎ ቀርቧል፡፡ አዲስ ጠጅ ባረጀአቁማዳ እንደማይጣል አምላካችንም ባልታደሰሕይወታቸው ሐዋርያትን እንዲጾሙ አላዘዛቸውም፡፡
ቀደም ሲል ጾም ሥጋን ለጊዜው ደስ ባለማሰኘቱበኀዘን እንደሚመሰል ተመልክተን ነበር፡፡ አሁንደግሞ በዚህ ምሳሌ ጾም ነፍስን ደስ የሚያሰኝበመሆኑ በወይን ተመስሎ አገኘነው፡፡ ‹‹ወይንየሰውን ልብ ደስ ያሰኛል›› እንዲል፡፡ (መዝ103.15)
ጠጅ ጣዮች ሲጥሉ (ሲጠምቁ) ተመልክታችሁታውቃላችሁ? አስቀድመው ቦታ ያዘጋጁለታል፡፡እግር እንዳይበዛበትም ጥላ እንዳይወድቅበትምይጠነቀቃሉ፡፡ እንዳይነፍስበትም ቀን ከሌሊትይተጉለታል፡፡ በመጨረሻ ሥራው አልቆ ሳለ ጠጁከደረቀ (ከጠነከረ) ይላላ ብለው ማር ያልሱታል(ይበርዙታል)፡፡ ከላላ ደግሞ ይድረቅ ብለው ጊዜይሰጡታል፡፡
በጠጅ ለተመሰለ ለጾምም በዓይነቱ ተመሳሳይከጥቅሙ አኳያ ደግሞ የበለጠ ጥንቃቄ ሊደረግለትያስፈልጋል፡፡ ለጠጅ ቦታ እንደሚዘጋጅለት ለጾምምሰውነትን ማዘጋጀትና ጊዜና ዕለት ወስኖ መመደብበአጠቃላይ ጾምን ማወጅ ይገባል፡፡ ስንዱ እመቤትቤተ ክርስቲያናችን የአጽዋማት ዐዋጅ ስላላት እኛየኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች የዚህ ችግርየለብንም፡፡ ለጠጅ እግር እንዳይበዛበትና ጥላእንዳይድቅበት እንደሚጠነቀቁለት ጾማችንምበከንቱ ውዳሴ አጋንንት እንዳይገቡበትና ያለመልካም ሥራ በጾም ብቻ ቀርተን ዋጋውእንዳያንስብን እየተጠነቀቅን መጾም ይገባናል፡፡ጠጅ ደረቀ ይላላ፤ ላላ ይድረቅ እንደሚባል ጾማችንበሕግ ከተሠራልን በላይ ሰዓቱ እንዳይበዛናከዓቅማችን በላይ አልፎ ሰውነታችን እንዳይጎዳ፤እንደዚሁም የአጽዋማትን ሰዓት ሳንጠብቅ ቀርተንምመንፈሳዊ ሕይወታችን እንዳይላላ ማዕከላዊውንስፍራ ይዘን በሕገ ቤተ ክርስቲያን መሠረትበጥንቃቄ መጾም እንደሚገባን ይህ ሦስተኛውምሳሌ ያስረዳናል፡፡
ይህን ትምህርት ጌታችን መድኃኒታች ኢየሱስክርስቶስ የሚቋጨው ‹‹አዲሱን የወይን ጠጅበአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል ሁለቱም ይጠባበቃሉ፡፡››በሚለው ኃይለ ቃል ነው፡፡ ዐረፍተ ነገሩ አዲስየወይን ጠጅ መጣል ያለበት በአዲስ አቁማዳመሆኑን ይናገራል፡፡ ስለዚህ ሐዋርያት ሕይወታቸውበጸጋ መንፈስ ቅዱስ ከታደሰ በኋላ በአዲሱአቁማዳቸው አዲሱን ወይን ጣሉ፡፡ ማለትምበአዲስ ሕይወት የአዲስ ኪዳንን ጾም (ጾመሐዋርያትን) መጾም ጀመሩ፡፡
አዲስ የወይን ጠጅ በአሮጌ አቁማዳ ሲጣልያፈነዳዋል፡፡ በአዲስ አቁማዳ ሲጣል ግን ያለፋዋልእንጂ ሊያፈነዳው አይችልም፡፡ ስለዚህ ወይኑምአቁማዳውም አዲስ የሆኑ እንደሆነ አቁማዳውወይኑን ያፈላዋል፡፡ ወይኑ ደግሞ አቁማዳውንያለፋዋል፡፡ በዚህ ጊዜ ‹‹ሁለቱም ይጠባበቃሉ››የሚለው ቃል ይፈጸማል፡፡
ጾምና ሰውነት እንደ ወይንና አቁማዳ ናቸው፡፡ወይንና አቁማዳ እንደሚጠባበቁ(እንደሚጠቃቀሙ) ጾምና ሰውነትም እንዲሁናቸው፡፡ ሰው የጾም ሕግን ቢጠብቅ ሕግም እርሱንትጠብቀዋለች፡፡ ‹‹ይጠባበቃሉ›› የተባለው ለዚህነው፡፡ ይህን የሚያስረዳ ‹‹አኮ ንሕነ ዘነዓቅቦሙለሕገጋት አላ እማንቱ ሕገጋት የዓቅቡነ ለዓቂብወለተፀውኖ›› የሚል ቃል ይገኛል፡፡ ይህም‹‹ሕጎችን እኛ አንጠብቃቸውም፡፡ እነርሱ መጠበቅንይጠብቁናል፤ መጠጊያም ይሆኑናል እንጂ፡፡›› እንደማለት ነው፡፡
ወይኑ ቆዳውን ማልፋቱ መልካም ነገር ነው፡፡ የለፋቆዳ ብዙ አገልግሎት ስላለው ይፈለጋልና፡፡ ለቀበቶ፣ለቦርሳ፣ ለጫማና ለልብስ የሚሆነው የለፋ ቆዳነው፡፡ የጾምም ጥቅም እዚህ ላይ ነው፡፡ ለልዩ ልዩአገልግሎትና ጥቅም የሚውል መንፈሳዊ ሕይወትእንዲኖረን ከፈለግን በጾም የለፋ (የደከመ) ሰውነትያስፈልገናል፡፡ ቆዳን ማልፋት ማዘጋጀት እንጂከጥቅም ውጭ ማድረግ አይደለም፡፡ ሰውነትንበጾም ማድከምም ለመንፈሳዊ ሥራ ማዘጋጀትእንጂ እንዳይሠራ ማድረግ እንዳልሆነ መረዳትያስፈልጋል፡፡ የታረሰ መሬት ለዘር እንደሚመችበጾም የደከመ ሰውነትም ለመንፈሳዊ ጉዞይመቻል፡፡ ቅዱስ ዳዊት ‹‹ጉልበቶቼ በጾም ደከሙ››ያለው ለዚህ ነው፡፡ (መዝ108.24)
ይህን የመሰለ ምሥጢር ያለውን ጾም‹‹የሽማግሌዎች ጾም፣ ከጥንት ያልነበረ›› እያሉበመጽሐፍ እና በቀኖና የሌላ ስም በመስጠትምእመናን እንዳይጾሙት ማድረግ የዲያብሎስትጥቅ የማስፈታት ዘዴ እንጂ ሌላ ምን ሊሆንይችላል?
ላለመጾም ምክንያት ከመፍጠር ምክንያት ፈጥሮመጾም በእጅጉ ይጠቅማል፡፡ ደሀው ድኅነት ራሱጾም ነው ካለ፤ ሌላው ኢትዮጵያ ውስጥ መኖር ራሱጾም ነው ካለ ለመጾም ክርስቲያን መሆን ሳይሆንሀገር ወይም ዜግነት መቀየር ሊያስፈልግ ነውማለት ነው? ምእመናን ‹‹ይህ የሽማግሌዎች ጾምነው›› ካሉ ስለ ጾም ማስተማርና ጾመው ማሳየትየሚጠበቅባቸው ‹‹ሰባክያን›› ደግሞ ‹‹ቃለእግዚአብሔር ይመትር ነደ እሳት›› እያሉ ጾም  ሽሮለመብላት ጥቅስ ከጠቀሱ ጾምን በጽሑፍ እንጂበሥራ ላናውቃት ነው ማለት ነው፡፡
ሐዋርያት እንደታዘዙት ዓለምን ሁሉ ለማስተማርከመሰማራታቸው በፊት መጀመሪያ ያደረጉት ጾምንነው፡፡ ሐዋርያት አልጾሙም ማለት ከላይየተብራራው የኢየሱስ ክርስቶስ ትንቢትና ምሳሌሐሰት ሆነ ማለት ነው፡፡ ሎቱ ስብሐት! ቃሉምተፈጽሟል ሐዋርያትም ጾመዋል፡፡ እኛም ጾሙንጾመን የምናስበውና የምንሠራው በጎ ሥራ ሁሉይከናወንልን ዘንድ ፈጣሪ በረድኤት አይለየን!
"መልካም ጾም ይሁንልን።"
ወስብሐትለእግዚአብሔር!

ረቡዕ 19 ጁን 2019

አርባእቱ እንስሳ

አርባዕቱ እንስሳ

ኪሩቤል ሱራፌል የተባሉት የልዑል እግዚአብሔርን ዙፋን በፍርሀት በረዐድ ኹነው የሚሸከሙ መላእክት ሲኾኑ ነቢዩ ኢሳይያስም ዙፋኑን እንደሚሸከሙ በምዕ ፴፯፥፲፮ ላይ “አቤቱ በኪሩቤል ላይ የምትቀመጥ የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ ሆይ አንተ ብቻኽን የምድር መንግሥታት ኹሉ አምላክ ነኽ ሰማይንና ምድርን ፈጥረኻል” በማለት ሲናገር፤ ነቢዩ ሕዝቅኤልም በፍርሀት ኹነው ሱራፌል ኪሩቤል (አርባዕቱ እንስሳት) ዙፋኑን እንደተሸከሙ ኾኖ አይቷል (ሕዝ ፲፥፩-፳፪፤ ፲፩፥፳፪)፡፡ “የሚሸከሙት” ሲባል ግን በጸጋ የሚያድርባቸው፣ የሚቀድሱት፣ ዙፋኑን ተሸክመው ይታያሉና እንዲኽ ተባለ እንጂ “ይጸውር ድደ ወይነብር ጠፈረ ኲሉ እኁዝ ውስተ እራኁ ወአጽናፈ ዓለም በእዴሁ” ማለት (በጠፈር ተቀምጦ መሠረትን ይሸከማል፤ ኹሉ በመኻል እጁ የተያዘ የዓለም ዳርቾችም በእጁ ያሉ) እንዲለው የሚሸከማቸውስ ርሱ ነው፡፡ጌታችን እሳታውያን በኾኑ በኪሩቤል ዠርባ ላይ ተቀምጦ በአንድነት በሦስትነት እንደሚቀደስ ቅዱሳት መጻሕፍት በስፋት ያስተምራሉ ዳዊትም “በኪሩቤልም ላይ ተቀምጦ በረረ በነፋስም ክንፍ በረረ” (መዝ ፲፰፥፲) በማለት ሲገልጽ፤ ዳግመኛም በየማነ አብ በዘባነ ኪሩብ ተቀምጦ የሚመሰገነው የእግዚአብሔር ልጅ የእስራኤል ዘነፍስ ጠባቂ ሊቀ ኖሎት ተገልጾ እንዲያድናቸው “ዮሴፍን እንደ መንጋ የምትመራ፥ የእስራኤል ጠባቂ ሆይ፥ አድምጥ በኪሩቤል ላይ የምትቀመጥ ተገለጥ” በማለት የናፍቆት ልመናን ይለምን ነበር (መዝ ፸፱፥፩)፡፡


ዮሐንስም በራእዩ ላይ በፍርሀት ኹነው ዙፋኑን ስለሚሸከሙት ስለ አርባእቱ እንስሳ ሲገልጽ “በዙፋኑም ፊት ብርሌ የሚመስል የብርጭቆ ባሕር ነበረ፤ በዙፋኑም መኻከል በዙፋኑም ዙሪያ በፊትና በኋላ ዐይኖች የመሏቸው አራት እንስሶች ነበሩ፤ ፊተኛውም እንስሳ አንበሳን ይመስላል፤ ኹለተኛውም እንስሳ ጥጃን ይመስላል፤ ሦስተኛውም እንስሳ እንደ ሰው ፊት ነበረው፤ አራተኛውም እንስሳ የሚበርረውን ንስር ይመስላል፤ አራቱም እንስሶች እያንዳንዳቸው ስድስት ስድስት ክንፎች አሏቸው በዙሪያቸውና በውስጣቸውም ዐይኖች መልተውባቸዋል፤ ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ የነበረውና ያለ የሚመጣውም ኹሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ እያሉ ቀንና ሌሊት አያርፉም” በማለት የኪሩቤልን የማያቋርጥ ምስጋናቸውን ተናግሯል (ራእ ፬፥፮‐፯)፡፡


ሊቁ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ የሥነ ፍጥረት ነገር ተገልጾለት በጻፈው መጽሐፍ ላይ “ወለዳግም ጾታ ዐሠርቱ ስሞሙ ኪሩቤል ካህናተ ቅዳሴ ወውዳሴ እምታሕተ ሐቌሆሙ አሐዱ ወእምላዕለ ሐቌሆሙ አርባዕቱ እለ ግሉፋን በአዕይንት” ብሎ እንደገለጸው ኹለተኛውን አመስጋኞች የኾኑት ዐሥሩን ነገድ ስማቸውን ኪሩቤል ሲላቸው ከወገባቸው በታች አንድ ከወገባቸው በላይ አራት አድርጎ ሲፈጥራቸው ዐይናቸው ብዙ ነው፤ ይኽም ኀላፍያትን መጻእያትን በማወቃቸው ይተረጐማል፤ አለቃቸው ኪሩብ ሲኾን የሰው መልክና የአንበሳ መልክ ያለው ነው፡፡ ሦስተኛውን ዐሥሩን ነገድ ስማቸውን ሱራፌል ሲላቸው የእነዚኽ አለቃቸው የንስር መልክና የእንስሳ መልክ ያለው ሲኾን ሱራፊ ሲባል ሲፈጥራቸውም ስድስት ስድስት ክንፍ አድርጎ ፈጥሯቸዋል (ሕዝ ፩፥፬‐፲፩)


ሊቁ ኤጲፋንዮስም የሥነ ፍጥረትን ነገር በሚናገረው መጽሐፉ ላይ አኗኗራቸውን በጥልቀት ሲተነትነው “ወነሥአ እግዚአብሔር እምሰራዊተ ኪሩቤል ክልኤተ አርእስተ ዘውእቶሙ ገጸ ሰብእ ወገጸ አንበሳ ወዓዲ ነሥአ እግዚአብሔር እምሰራዊተ ሱራፌል ክልኤተ ክልኤተ አርእስተ ዘውእቶሙ ገጸ ንስር ወገጸ እንስሳ ወለክኦሙ መልዕልተ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት በማእዘንተ መርሕባ ለአርያም ወሰፍሐ ዲበ ዘባናቲሆሙ ሰማየ ዘሕብሩ በረድ” ይላል ከነገደ ኪሩቤል ኹለት ገጸ ሰብእ እና ገጸ አንበሳን ከሱራፌል ኹለት ገጸ ንስርና ገጸ እንስሳን አንሥቶ ከኢየሩሳሌም ሰማያዊት በላይ ከሰማይ ውዱድ በታች አቁሞ በነርሱ ላይ ሰማይ ውዱድን እንደ መረሻት ጫነባቸው፤ በላይም ሕብሩ በረድ የመሰለውን ዙፋን እንደ ሠረገላ ጭኖባቸዋል፤ እነዚኽንም በምሥራቅ፣ በምዕራብ፣ በሰሜን፣ በደቡብ በአራቱ መኣዝን ዠርባቸውን ወደ ውስጥ ፊታቸውን ወደ ውጪ እያደረገ አቁሟቸዋል፤ ነቢዩ ሕዝቅኤል ስለዚኽ ነገር በምዕ ፩፥፲፪ ላይ “እያንዳንዱም ወደ ፊት ቀጥ ብሎ ይኼድ ነበር መንፈስም ወደሚኼድበት ኹሉ ይኼዱ ነበር፥ ሲኼዱም አይገላመጡም ነበር” በማለት እንደተናገረ ገጽ ለገጽ ሳይተያዩ ሥላሴ በፈቀዱት ፍኖት አንዱ በኼደበት ሦስቱ እየተከታተሉ ይኼዳሉ፡፡


እነዚኽንም እንደ ነቢዩ ሕዝቅኤል ገለጻ ፲፮ ሲኾኑ የቀሩት ከውስጥ ስለኾኑ ስለማይታዩ አራቱ ግን ብቅ ብቅ ብለው ስለሚታዩ ዮሐንስ አራት ብሏቸዋል እንጂ እንደ ሕዝቅኤል ገጻቸው ፲፮ ነው፡፡ ሊቁ “እምርእሶሙ እስከ ሐቌሆሙ አርባዕቱ ወእምሐቌሆሙ እስከ እግሮሙ አሐዱ ከመ ርእየተ እለ ቄጥሩ ዘውእቱ ዖፍ ዘይነብር በሀገረ ፋርስ” እንዲላቸው፤ ሊቁ ቅዱስ ያሬድም በመጽሐፈ ድጓው ላይ “ከመ ርእየተ እለቄጥሩ ገጸ በገጽ ኢይትናጸሩ” ብሎ እንደገለጻቸው በፋርስ ሀገር የሚኖረው እለቄጥሩ የተባለውን ዎፍ ከወገቡ በታች አንድ ከወገቡ በላይ አራት እንደኾነ እነዚኽንም ከወገባቸው በታች አንድ ከወገባቸው በላይ አራት አድርጎ ፈጥሯቸዋል፤ የገጸ ሰብእ አቋቋሙ በምሥራቅ አተያዩ ወደ ምዕራብ ነው፤ የገጸ አንበሳ አቋቋሙ በምዕራብ አተያዩ ወደ ምሥራቅ፤ የገጸ ላሕም አቋቋሙ በሰሜን አተያዩ ወደ ደቡብ፤ የገጸ ንስር አቋቋሙ በደቡብ አተያዩ ወደ ሰሜን ሲኾን ገጽ ለገጽ አይተያዩም፡፡


የሰው መልክ ያለው ስለ ሰው ፍጥረት ይለምናል፤ የአንበሳ መልክ ያለው ስለ አራዊት ይለምናል፤ የንስር መልክ ያለው ስለ አዕዋፍ ይለምናል፤ የላም መልክ ያለው ስለ እንስሳ የሚለምን ሲኾን ከመላእክት ኹሉ ይልቅ በእግዚአብሔር ዘንድ በባለሟልነት የቀረቡ ናቸው፡፡ በኢሳ ፮፥፩-፫ ላይ፡- “ንጉሡ ዖዝያን በሞተበት ዓመት እግዚአብሔርን በረዥምና ከፍ ባለ ዙፋን ላይ ተቀምጦ አየኹት የልብሱም ዘርፍ መቅደሱን መልቶት ነበር፤ ሱራፌልም ከርሱ በላይ ቆመው ነበር ለእያንዳንዱም ስድስት ክንፍ ነበረው በኹለት ክንፍ ፊቱን ይሸፍን ነበር በኹለቱም ክንፍ እግሮቹን ይሸፍን ነበር በኹለቱም ክንፍ ይበር ነበር፤ አንዱም ለአንዱ ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ምድር ኹሉ ከክብሩ ተመልታለች እያለ ይጮኽ ነበር” ይላል ይኽ መሸፈናቸው ያድናቸዋል ቢሉ? ትእምርተ ፍርሀት ነው፤ ዛሬ በዚኽ ዓለም ሴቶችን ሕፃናትን እንመታችኋለን ባሏቸው ጊዜ እጃቸውን መጋረዳቸው የሚያድናቸው ኾኖ ሳይኾን ትእምርተ ፍርሀት እንደኾነ ኹሉ፡፡


አንድም በኹለት ክንፋቸው ፊታቸውን መሸፈናቸው ፊትኽን ማየት አይቻለንም ሲሉ በኹለት ክንፋቸው እግራቸውን መሸፈናቸው ከፊትኽ መቆም አይቻለንም ሲሉ፤ ኹለት ክንፋቸውን ወዲያና ወዲኽ ያደርጋሉ አለ ትእምርተ ተልእኮ ነው፡፡ አንድም በኹለት ክንፋቸው ፊታቸውን መሸፈናቸው ባሕርይኽን መመርመር አይቻለንም ሲሉ፤ በኹለት ክንፋቸው እግራቸውን መሸፈናቸው ባሕርይኽን መረማመድ መተላለፍ አይቻለንም ሲሉ፤ ኹለት ክንፋቸውን ወዲያ ወዲኽ ያደርጋሉ ከእእምሮ ወደ አእምሮ ለመፋለሳቸው፡፡አንድም ኹለት ክንፋቸውን ወደ ላይ አድርገው ይታያሉ አለ ወደላይ ቢወጡ ቢወጡ አትገኝም ሲሉ፤ ኹለት ክንፋቸውን ወደታች አድርገው ይታያሉ ወደታች ቢወርዱ ቢወርዱ አትገኝም ሲሉ፤ ክንፋቸውን ወዲያና ወዲኽ ያደርጋሉ ወዲያና ወዲኽ ቢሉ አትገኝም ሲሉ፤አንድም ወደላይ መዘርጋት በሰማይ ምሉእ ነኽ ሲሉ ወደታች መዘርጋቸው በምድርም ምሉእ ነኽ ሲሉ፤ ወዲያና ወዲኽ መዘርጋታቸው በኹሉ ምሉእ ነኽ ማለታቸው ነው፤

አንድም ወደላይ መዘርጋት ትእምርተ ተመስጦ ወደታች መዘርጋት ትእምርተ ትሕትና፤ ወዲያና ወዲኽ ረብቦ መታየት ትእምርተ ተልእኮ ነው፤


በአጠቃላይ ኹለት ክንፋቸውን ወደላይ ኹለት ክንፋቸውን ወደታች ኹለት ክንፋቸውን ወዲያና ወዲኽ አድርገው ትእምርተ መስቀል መሥራታቸው በብሉይ ኪዳን ከኾነ እንዲኽ ባለ መስቀል ተሰቅለኽ ዓለምን ታድነዋለኽ ሲሉ በዘመነ ሐዲስ የኾነ እንደኾነ እንዲኽ ባለ ትእምርተ መስቀል ተሰቅለኽ ዓለምን አድነኸዋል ሲሉ ነው፡፡


የእነዚኽ አርባዕቱ እንስሳ ፊታቸው በርካታ ምስጢራትን ሲያመለክቱ ገጸ ሰብእ በማቴዎስ፤ ገጸ አንበሳ በማርቆስ፤ ገጸ ላሕም በሉቃስ፤ ገጸ ንስር በዮሐንስ ተመስሏል፤ በሌላ ምስጢር የሰው ገጽ ያለው የጌታን ሰው የመኾንን ነገር፤ የላም መልክ ያለው በቀራንዮ ላይ ደሙን ማፍሰሱ፤ የአንበሳው መልክ ያለው የጌታችንን ትንሣኤ፤ የንስር መልክ ያለው የጌታን ዕርገት እንደሚያመለክቱ መተርጒማን ይተነትኑታል፤ዐምደ ሃይማኖት አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም እጅግ ምጡቅ በኾነው ዕውቀቱ ዕጓለ አንበሳ የተባለው የወልድ የባሕርይ አባቱን አብን በአንበሳ ይመስለዋል፤ ሥጋን ተውሕዶ ፍጹም ሰው የኾነው ወልድን የሰው መልክ ባለው መስሎ ገልጾታል፡፡ በአምሳለ ርግብ ወርዶ በወልድ ራስ ላይ ተቀምጦ የታየው መንፈስ ቅዱስን የንስር መልክ ባለው መስሎ አብራርቶ ጽፎታል፤ በቀንዱ የማይበራታ ላሕም ተብሎ የተመሰገነው የወልደ እግዚአብሔር ቅዱስ ሥጋው የሚፈትትባት፤ ክቡር ደሙ የሚቀዳባት በአራቱ ኪሩቤል አምሳል አራት መአዝን ያላት ቤተ ክርስቲያንን በገጸ ላሕም አምሳል ገልጦ አመስጥሮታል፡፡

ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድም በድጓው ላይ፡-

“አርባእቱ እንስሳ በእንቲኣነ ጸልዩ
ኢይልክፈነ ለእሳት ዋዕዩ
እንስሳ አርባዕቱ መናብርቲሁ ለዋሕድ
መተንብላን ለኲሉ ትውልድ”

(አራቱ እንስሳ የሲኦል እሳት ግለቱ እንዳይነካን ስለ እኛ ጸልዩ፤ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለውን አምላክ ዙፋኖቹ የኾኑ አራቱ እንስሳ ለትውልድ ኹሉ አማላጅ ናቸው) በማለት አንደተማፀነ እኛም የአምላካችንን ዙፋን የሚሸከሙ እነዚኽን ግሩማን መንፈሳውያን መላእክትን ከጌታችን ከአምላካችን ከክርስቶስ እንዲያማልዱን እንለምናለን፡፡

መጽሐፈ ሰዓታት ንባቡና ትርጓሜው ከሚለው መጽሐፌ የተወሰደ

የቤተክርስቲያን ትርጓሜ ምን ይላል ሊንኩን ይጫኑ። 

ሐሙስ 23 ሜይ 2019

መቅድም

የሰንበት ትምህርት ቤት

እግዚአብሔር አምላክ የሰውንልጅ በአርያውና በአምሳሉከፈጠረ በኋላ ሰው ከፈጣሪውጋር በጥብቅ እንዲናገናኝ ልዩልዩ የአገልግሎት መንገዶችንአዘጋጀ። እያንዳንዱ በተሰጠውመክሊት ያተርፍና በጸጋውያገለግል ዘንድ በመጀመርያዕድሜው በፈቀደለት ሁሉመማርና ማገልገልይኖርበታል። እግዚአብሔርአምላክ መመለክ በአለበትአግባብ ለማምለክ እምነትያስፈልጋል፤ ከእምነትእንዳንወጣ ደግሞስለምናምነው ነገር በቂዕውቀት ሊኖረን ይገባል፤እምነትን፣ ተስፋና ፍቅርን ሰንቆእስከመጨረሻ ድረስ ለመጽናትመንፈሳዊ ዕውቀት መሠረታዊነው።

“ህዝቤ ዕውቀት በማጣትጠፍቷል” (ሆሴ 4፥6)የተባለው በእኛ ላይእንዳይፈጸም ዕድሜያችንበሚፈቅድልን ሁሉ ሃይማኖታዊዕውቀትን እንድንማር ቤተክርስቲያን በቅዱሳን ጸሎትበእግዚአብሔር መልካምፍቃድ ሰንበት ት/ቤትንአቋቋመች። ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ልጆቿ ጽድቅንይማሩ ዘንድ በሰንበት ት/ቤትአሰባስባ ቃለ እግዚአብሔርንአውቀው፣ ባሕርየእግዚአብሔርን ተረድተውእንዲያመልኩ፣ ሕጉንጠብቀው፣ በሃይማኖት፣በምግባርና በትሩፋት ፀንተውአምላካቸውን መስለውእንዲኖሩ የእርሱ የሆነችውንመንግስተ እግዚአብሔርንእንዲወርሱ በብሉይ ከአምላኳየተቀበለችውን ሕግጋተእግዚአብሔርን አስተምራበሐዲስ ኪዳንም በ40 እናበ80 ቀን እያጠመቀችለምዕመናን እንደ እድሜያቸውእና እንደ አዕምዕሮብስለታቸው ቃለእግዚአብሔርን ደከመኝ ሰለቸኝሳትል ታስተላልፋለች።በስብከት፣ በዝማሬ፣ በቅዳሴ፣በስዓታት፣ በማሕሌት የቅኔውንምሥጢር በትርጓሜእያስተማረች ምዕመናንንበእምነት አንፃ ለመንግስተሰማያት እያዘጋጀች ዛሬ ላይደርሳለች።

ከስሙ እንደምንረዳው ሰንበትትምህርት ቤት ማለት የጾታልዩነት ሳይደረግ የቤተክርስቲያን ተተኪ ትውልድወይም መንፈሳዊ ወጣቶችበዕለተ ሰንበት፣ በዓበይትበዓላትና አመቺ በሆነ ጊዜ ሁሉበአጥቢያ ቤተ ክርስቲያንእየተገኙ የቤተ ክርስቲያንንዶግማ፣ቅኖና፣ሥርዓትናትውፊት የሚማሩበት እናበእምነት፣በምግባርናበሃይማኖት ጸንተው ይኖሩዘንድ መንፈሳዊ ሕይወታቸውንየሚያጠነክሩበት ትምህርትቤት ነው:: መንፈሳዊ ወጣቶችየሚባሉት የኢትዮጵያኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ትምህርተሃይማኖት፣ ሥርዓትና ትውፊትበዕድሜ ክልላቸው የሚማሩየቤተ ክርስቲያን አባላት ናቸው(ቃለ ዓዋዲ ፲፱፻፺፩)።

በመጽሐፍ ቅዱስ ሰንበት ት/ቤት ተብሎ የተፃፈ ቀጥተኛየሆነ ስም ባይገኝም ዛሬ ላይበሰንበት ት/ቤት የሚተገበረውመንፈሳዊ አገልግሎት ማለትምልጆችን በቤተ እግዚአብሔርማስተማር በብሉይ ኪዳንዘመንም ይፈጸም እንደነበርመጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳናል።የሰንበት ት/ቤት ፅንሰ ሀሳብምከዚያ የመነጨ ነው። “እነዚህንቃሎች በልባችሁና በነፍሳችሁአኑሩ እነርሱንም ለምልክትበእጃችሁ ላይ እሠሯቸውበዐይኖቻችሁም መካከል እንደክታብ ይሁን ልጆቻችሁንምአስተምሯቸው በቤትህምስትቀመጥ በመንገድምስትሄድ ስትተኛም ስትነሣምአጫውቱአቸው” (ዘዳ11÷18-21 )በማለትእስራኤላውያን ልጆቻቸውንሕግጋተ እግዚአብሔርእንዲያስተምሯቸው ታዘዋል፡፡እነርሱም ይህን አምላካዊ ቃልተግባራዊ ለማድረግልጆቻቸውን ወደ ቤተእግዚአብሔር እየላኩ እናበቤታቸው ውስጥም ተግተውያስተምሩ ነበር።

በሐዲስ ኪዳንምመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስበመዋዕለ ሥጋዌ ልዩ ትኩረትከሰጣቸው ቁም ነገሮችመካከል ሕፃናት ወደ ቤተክርስቲያን ይመጡ ዘንድ ነበር።ልበ ንጹሐንን በሕጻናት መስሎያስተማረበት አንቀጽምበመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ተጽፎይገኛል። ይህም በዘመናችንላለችው ቤተ ክርስቲያንየሕፃናት፣ የወጣቶች እናየጎልማሶች ማስተማሪያለሆነችው ሰንበት ትምህርትቤት መነሻ የሆነ እናመሠረቱም መጽሐፍ ቅዱሳዊመሆኑን ያረጋግጥልናል (ማቴ18፥3፣ 21፥16፣ ማር 9፥37)፡፡

የሰንበት ትምህርት ቤትአመሠራረት በኢትዮጵያስንመለከት ዘመናዊ ትምህርትቤት እየተስፋፋ ሲመጣ ወጣቱትውልድ ከአምልኮተእግዚአብሔር እንዳይለይ፤በተለይ ለዘመናዊ ትምህርትአስተማሪነት በመጡእራሳቸውን ”ኢየሱሳውያን”ብለው በሚጠሩ የውጭመምህራን ከመጡበትዓለማዊ ትምህርት ባሻገርየኑፋቄ ትምህርትማሰራጨታቸው፣ በተቃራኒውደግሞ ወደ አብነት ትምህርትቤት የሚሄደው ወጣት ቁጥርበመቀነሱ ምክንያት በ20ኛውክፍለ ዘመን ወጣቱን ለመያዝመንፈሳዊ መርሐ ግብሮችናየማኅበራት እንቅስቃሴዎችተጀመሩ። እነዚህ የተጀመሩመርሐ ግብሮችና ማኅበራትየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶቤተ ክርስቲያንአስተምህሮዎቿ ሳይበረዙለትውልድ እንዲተላለፉ በተለይበሕጻናት እና በወጣቶች ላይትኩረት ሰጥው እንዲሠሩትልቁን ድርሻ ወስደዋል።

በዚህም መሠረት ሰንበትትምህርት ቤት በማቋቋምትውልድን በኦርቶዶክሳዊሃይማኖት የማነጽ፣ ዶግማን፣ቀኖናን እና ትውፊትንማስተማር ተጀመረ። በ1960ዓ.ም ይህን የሰንበት ትምህርትቤቶች እንቅስቃሴለማስተባበር እና ለማጠናከርይቻል ዘንድ በጠቅላይ ቤተክህነት በስብከተ ወንጌልናማስታወቂያ መምሪያ ሥርማእከላዊ ጽ/ቤት በዋናነትተቋቁሞ ስያሜውም የሰንበትት/ቤት መምህራን ጽሕፈት ቤትተብሎ ተሰይሟል፡፡ ይህአካሄድ እያደገ ሲመጣበ1965 ዓ.ም ራሱን ችሎ ወደወጣቶች ጉዳይ መምሪያነትእንዲያድግ ተደርጓል፡፡ ዛሬ ላይየሰንበት ትምህርት ቤትማደራጃ መምርያ የሚልሰንበት ትምህርት ቤቶችንየሚያደራጅና የሚመራበተቋም ደረጃ ትልቅ መምርያተቋቁሞ አገልግሎቱንእየፈጸመ ይገኛል።

የሰንበት ት/ቤት ጥቅሙናአስፈላጊነቱ የጎላ መሆኑበተግባር በመረጋገጡበ1970 ዓ.ም “ሰንበት ት/ቤት” በሚል ስያሜ ሕጋዊ ሆኖእንዲቀጥል እና በሁሉምአብያተ ክርስቲያናት ውስጥሰንበት ት/ቤቶች እንዲቋቋሙየተቋቋሙትም እንዲጠናከሩተሻሽሎ በወጣው ቃለ ዓዋዲእንዲጸድቅ ተደርጓል፡፡ የሰ/ት/ቤት አገልግሎትን የበለጠለማጠናከር ሰንበት ት/ቤቶችየሚመሩበትን መተዳደሪያደንብ አጽድቆ ሥራ ላይእንዲውል ያደረገ ሲሆን አሁንአስካለንበት ዘመን ድረስሰንበት ት/ቤቶች ይህንመመሪያ ከዋናው ቃለ ዐዋዲጋር በማስተባበርእየተመሩበትና ዘርፈ ብዙአገልግሎቶችን እየፈፀሙይገኛሉ፡፡

ይህን ወጣቱን ትውልድበዘመናዊነት ተፅዕኖ ውስጥወድቆ ከመንፈሳዊ ሕይወትእንዳይወጣ ልዩ ክትትልበማድረጉ ረገድ ኢትዮጵያ ብቻሳትሆን እኅት አብያተክርስቲያናትም ሰንበትትምህርት ቤትን አቋቁመውአገልግሎት መስጠት ከጀመሩብዙ ዓመታትን አስቆጥረዋል።በተለይ ግብፅና ሕንድበተደራጀ መልኩ እየሠሩበትይገኛሉ።

የሰንበት ትምህርት ቤትየተቋቋመበት ዋና ዓላማ

የሰንበት ትምህርት ቤትዓላማ፦

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንዶግማ፣ ቅኖና፣ እምነትናሥርዓት ተጠብቆሳይበረዝ ሳይከለስከትውልድ ወደ ትውልድእንዲተላለፍ ማድረግ

ማንኛውም የቤተክርስቲያኒቱ ተከታይ የሆነምእመን የሃይማኖቱንሥርዓት በውልእንዲያውቅና እንዲረዳማድረግ

ወጣቶች የቤተክርስቲያንን ሕግና ሥርዓትተምረው ለሀገርና ለወገንጠቃሚ፣ መልካምና በሥነምግባር የታነፁ ዜጎችእንዲሆኑ ማድረግ

በጉብዝናህ ወራትፈጣሪህን አስብ (መክ.፲፪፡፩) የሚለውን የአምላክተእዛዝ ወጣቶችእንዲፈጽሙ ማስቻል

እነዚህን ከላይ የተዘረዘሩትንአበይት ዓላማዎች ከግብለማድረስ ጠንካራ ሰንበትትምህርት ቤት ያስፈልጋል።ወጣቶችን በሰንበት ትምህርትቤት ለማሳደግ ከጠቅላይ ቤተክህነት እስከ አጥቢያ አብያተክርስቲያናት ሁሉም ባለ ድርሻአካላት የበኩላቸውን መወጣትበእጅጉ አስፈላጊ ነው።አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስለቅዱስ ጴጥሮስ ከሰጠውመመርያና ትዕዛዝ መካከልሕፃናትንና ወጣቶችንበሃይማኖት እያስተማረለመንግስተ ሰማያት ማብቃት

ተከታዮች