ሐሙስ 20 ጁን 2019
ጾመ ሐዋርያት
ረቡዕ 19 ጁን 2019
አርባእቱ እንስሳ
አርባዕቱ እንስሳ
ኪሩቤል ሱራፌል የተባሉት የልዑል እግዚአብሔርን ዙፋን በፍርሀት በረዐድ ኹነው የሚሸከሙ መላእክት ሲኾኑ ነቢዩ ኢሳይያስም ዙፋኑን እንደሚሸከሙ በምዕ ፴፯፥፲፮ ላይ “አቤቱ በኪሩቤል ላይ የምትቀመጥ የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ ሆይ አንተ ብቻኽን የምድር መንግሥታት ኹሉ አምላክ ነኽ ሰማይንና ምድርን ፈጥረኻል” በማለት ሲናገር፤ ነቢዩ ሕዝቅኤልም በፍርሀት ኹነው ሱራፌል ኪሩቤል (አርባዕቱ እንስሳት) ዙፋኑን እንደተሸከሙ ኾኖ አይቷል (ሕዝ ፲፥፩-፳፪፤ ፲፩፥፳፪)፡፡ “የሚሸከሙት” ሲባል ግን በጸጋ የሚያድርባቸው፣ የሚቀድሱት፣ ዙፋኑን ተሸክመው ይታያሉና እንዲኽ ተባለ እንጂ “ይጸውር ድደ ወይነብር ጠፈረ ኲሉ እኁዝ ውስተ እራኁ ወአጽናፈ ዓለም በእዴሁ” ማለት (በጠፈር ተቀምጦ መሠረትን ይሸከማል፤ ኹሉ በመኻል እጁ የተያዘ የዓለም ዳርቾችም በእጁ ያሉ) እንዲለው የሚሸከማቸውስ ርሱ ነው፡፡ጌታችን እሳታውያን በኾኑ በኪሩቤል ዠርባ ላይ ተቀምጦ በአንድነት በሦስትነት እንደሚቀደስ ቅዱሳት መጻሕፍት በስፋት ያስተምራሉ ዳዊትም “በኪሩቤልም ላይ ተቀምጦ በረረ በነፋስም ክንፍ በረረ” (መዝ ፲፰፥፲) በማለት ሲገልጽ፤ ዳግመኛም በየማነ አብ በዘባነ ኪሩብ ተቀምጦ የሚመሰገነው የእግዚአብሔር ልጅ የእስራኤል ዘነፍስ ጠባቂ ሊቀ ኖሎት ተገልጾ እንዲያድናቸው “ዮሴፍን እንደ መንጋ የምትመራ፥ የእስራኤል ጠባቂ ሆይ፥ አድምጥ በኪሩቤል ላይ የምትቀመጥ ተገለጥ” በማለት የናፍቆት ልመናን ይለምን ነበር (መዝ ፸፱፥፩)፡፡ዮሐንስም በራእዩ ላይ በፍርሀት ኹነው ዙፋኑን ስለሚሸከሙት ስለ አርባእቱ እንስሳ ሲገልጽ “በዙፋኑም ፊት ብርሌ የሚመስል የብርጭቆ ባሕር ነበረ፤ በዙፋኑም መኻከል በዙፋኑም ዙሪያ በፊትና በኋላ ዐይኖች የመሏቸው አራት እንስሶች ነበሩ፤ ፊተኛውም እንስሳ አንበሳን ይመስላል፤ ኹለተኛውም እንስሳ ጥጃን ይመስላል፤ ሦስተኛውም እንስሳ እንደ ሰው ፊት ነበረው፤ አራተኛውም እንስሳ የሚበርረውን ንስር ይመስላል፤ አራቱም እንስሶች እያንዳንዳቸው ስድስት ስድስት ክንፎች አሏቸው በዙሪያቸውና በውስጣቸውም ዐይኖች መልተውባቸዋል፤ ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ የነበረውና ያለ የሚመጣውም ኹሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ እያሉ ቀንና ሌሊት አያርፉም” በማለት የኪሩቤልን የማያቋርጥ ምስጋናቸውን ተናግሯል (ራእ ፬፥፮‐፯)፡፡
ሊቁ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ የሥነ ፍጥረት ነገር ተገልጾለት በጻፈው መጽሐፍ ላይ “ወለዳግም ጾታ ዐሠርቱ ስሞሙ ኪሩቤል ካህናተ ቅዳሴ ወውዳሴ እምታሕተ ሐቌሆሙ አሐዱ ወእምላዕለ ሐቌሆሙ አርባዕቱ እለ ግሉፋን በአዕይንት” ብሎ እንደገለጸው ኹለተኛውን አመስጋኞች የኾኑት ዐሥሩን ነገድ ስማቸውን ኪሩቤል ሲላቸው ከወገባቸው በታች አንድ ከወገባቸው በላይ አራት አድርጎ ሲፈጥራቸው ዐይናቸው ብዙ ነው፤ ይኽም ኀላፍያትን መጻእያትን በማወቃቸው ይተረጐማል፤ አለቃቸው ኪሩብ ሲኾን የሰው መልክና የአንበሳ መልክ ያለው ነው፡፡ ሦስተኛውን ዐሥሩን ነገድ ስማቸውን ሱራፌል ሲላቸው የእነዚኽ አለቃቸው የንስር መልክና የእንስሳ መልክ ያለው ሲኾን ሱራፊ ሲባል ሲፈጥራቸውም ስድስት ስድስት ክንፍ አድርጎ ፈጥሯቸዋል (ሕዝ ፩፥፬‐፲፩)
ሊቁ ኤጲፋንዮስም የሥነ ፍጥረትን ነገር በሚናገረው መጽሐፉ ላይ አኗኗራቸውን በጥልቀት ሲተነትነው “ወነሥአ እግዚአብሔር እምሰራዊተ ኪሩቤል ክልኤተ አርእስተ ዘውእቶሙ ገጸ ሰብእ ወገጸ አንበሳ ወዓዲ ነሥአ እግዚአብሔር እምሰራዊተ ሱራፌል ክልኤተ ክልኤተ አርእስተ ዘውእቶሙ ገጸ ንስር ወገጸ እንስሳ ወለክኦሙ መልዕልተ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት በማእዘንተ መርሕባ ለአርያም ወሰፍሐ ዲበ ዘባናቲሆሙ ሰማየ ዘሕብሩ በረድ” ይላል ከነገደ ኪሩቤል ኹለት ገጸ ሰብእ እና ገጸ አንበሳን ከሱራፌል ኹለት ገጸ ንስርና ገጸ እንስሳን አንሥቶ ከኢየሩሳሌም ሰማያዊት በላይ ከሰማይ ውዱድ በታች አቁሞ በነርሱ ላይ ሰማይ ውዱድን እንደ መረሻት ጫነባቸው፤ በላይም ሕብሩ በረድ የመሰለውን ዙፋን እንደ ሠረገላ ጭኖባቸዋል፤ እነዚኽንም በምሥራቅ፣ በምዕራብ፣ በሰሜን፣ በደቡብ በአራቱ መኣዝን ዠርባቸውን ወደ ውስጥ ፊታቸውን ወደ ውጪ እያደረገ አቁሟቸዋል፤ ነቢዩ ሕዝቅኤል ስለዚኽ ነገር በምዕ ፩፥፲፪ ላይ “እያንዳንዱም ወደ ፊት ቀጥ ብሎ ይኼድ ነበር መንፈስም ወደሚኼድበት ኹሉ ይኼዱ ነበር፥ ሲኼዱም አይገላመጡም ነበር” በማለት እንደተናገረ ገጽ ለገጽ ሳይተያዩ ሥላሴ በፈቀዱት ፍኖት አንዱ በኼደበት ሦስቱ እየተከታተሉ ይኼዳሉ፡፡
እነዚኽንም እንደ ነቢዩ ሕዝቅኤል ገለጻ ፲፮ ሲኾኑ የቀሩት ከውስጥ ስለኾኑ ስለማይታዩ አራቱ ግን ብቅ ብቅ ብለው ስለሚታዩ ዮሐንስ አራት ብሏቸዋል እንጂ እንደ ሕዝቅኤል ገጻቸው ፲፮ ነው፡፡ ሊቁ “እምርእሶሙ እስከ ሐቌሆሙ አርባዕቱ ወእምሐቌሆሙ እስከ እግሮሙ አሐዱ ከመ ርእየተ እለ ቄጥሩ ዘውእቱ ዖፍ ዘይነብር በሀገረ ፋርስ” እንዲላቸው፤ ሊቁ ቅዱስ ያሬድም በመጽሐፈ ድጓው ላይ “ከመ ርእየተ እለቄጥሩ ገጸ በገጽ ኢይትናጸሩ” ብሎ እንደገለጻቸው በፋርስ ሀገር የሚኖረው እለቄጥሩ የተባለውን ዎፍ ከወገቡ በታች አንድ ከወገቡ በላይ አራት እንደኾነ እነዚኽንም ከወገባቸው በታች አንድ ከወገባቸው በላይ አራት አድርጎ ፈጥሯቸዋል፤ የገጸ ሰብእ አቋቋሙ በምሥራቅ አተያዩ ወደ ምዕራብ ነው፤ የገጸ አንበሳ አቋቋሙ በምዕራብ አተያዩ ወደ ምሥራቅ፤ የገጸ ላሕም አቋቋሙ በሰሜን አተያዩ ወደ ደቡብ፤ የገጸ ንስር አቋቋሙ በደቡብ አተያዩ ወደ ሰሜን ሲኾን ገጽ ለገጽ አይተያዩም፡፡
የሰው መልክ ያለው ስለ ሰው ፍጥረት ይለምናል፤ የአንበሳ መልክ ያለው ስለ አራዊት ይለምናል፤ የንስር መልክ ያለው ስለ አዕዋፍ ይለምናል፤ የላም መልክ ያለው ስለ እንስሳ የሚለምን ሲኾን ከመላእክት ኹሉ ይልቅ በእግዚአብሔር ዘንድ በባለሟልነት የቀረቡ ናቸው፡፡ በኢሳ ፮፥፩-፫ ላይ፡- “ንጉሡ ዖዝያን በሞተበት ዓመት እግዚአብሔርን በረዥምና ከፍ ባለ ዙፋን ላይ ተቀምጦ አየኹት የልብሱም ዘርፍ መቅደሱን መልቶት ነበር፤ ሱራፌልም ከርሱ በላይ ቆመው ነበር ለእያንዳንዱም ስድስት ክንፍ ነበረው በኹለት ክንፍ ፊቱን ይሸፍን ነበር በኹለቱም ክንፍ እግሮቹን ይሸፍን ነበር በኹለቱም ክንፍ ይበር ነበር፤ አንዱም ለአንዱ ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ምድር ኹሉ ከክብሩ ተመልታለች እያለ ይጮኽ ነበር” ይላል ይኽ መሸፈናቸው ያድናቸዋል ቢሉ? ትእምርተ ፍርሀት ነው፤ ዛሬ በዚኽ ዓለም ሴቶችን ሕፃናትን እንመታችኋለን ባሏቸው ጊዜ እጃቸውን መጋረዳቸው የሚያድናቸው ኾኖ ሳይኾን ትእምርተ ፍርሀት እንደኾነ ኹሉ፡፡
አንድም በኹለት ክንፋቸው ፊታቸውን መሸፈናቸው ፊትኽን ማየት አይቻለንም ሲሉ በኹለት ክንፋቸው እግራቸውን መሸፈናቸው ከፊትኽ መቆም አይቻለንም ሲሉ፤ ኹለት ክንፋቸውን ወዲያና ወዲኽ ያደርጋሉ አለ ትእምርተ ተልእኮ ነው፡፡ አንድም በኹለት ክንፋቸው ፊታቸውን መሸፈናቸው ባሕርይኽን መመርመር አይቻለንም ሲሉ፤ በኹለት ክንፋቸው እግራቸውን መሸፈናቸው ባሕርይኽን መረማመድ መተላለፍ አይቻለንም ሲሉ፤ ኹለት ክንፋቸውን ወዲያ ወዲኽ ያደርጋሉ ከእእምሮ ወደ አእምሮ ለመፋለሳቸው፡፡አንድም ኹለት ክንፋቸውን ወደ ላይ አድርገው ይታያሉ አለ ወደላይ ቢወጡ ቢወጡ አትገኝም ሲሉ፤ ኹለት ክንፋቸውን ወደታች አድርገው ይታያሉ ወደታች ቢወርዱ ቢወርዱ አትገኝም ሲሉ፤ ክንፋቸውን ወዲያና ወዲኽ ያደርጋሉ ወዲያና ወዲኽ ቢሉ አትገኝም ሲሉ፤አንድም ወደላይ መዘርጋት በሰማይ ምሉእ ነኽ ሲሉ ወደታች መዘርጋቸው በምድርም ምሉእ ነኽ ሲሉ፤ ወዲያና ወዲኽ መዘርጋታቸው በኹሉ ምሉእ ነኽ ማለታቸው ነው፤
አንድም ወደላይ መዘርጋት ትእምርተ ተመስጦ ወደታች መዘርጋት ትእምርተ ትሕትና፤ ወዲያና ወዲኽ ረብቦ መታየት ትእምርተ ተልእኮ ነው፤
በአጠቃላይ ኹለት ክንፋቸውን ወደላይ ኹለት ክንፋቸውን ወደታች ኹለት ክንፋቸውን ወዲያና ወዲኽ አድርገው ትእምርተ መስቀል መሥራታቸው በብሉይ ኪዳን ከኾነ እንዲኽ ባለ መስቀል ተሰቅለኽ ዓለምን ታድነዋለኽ ሲሉ በዘመነ ሐዲስ የኾነ እንደኾነ እንዲኽ ባለ ትእምርተ መስቀል ተሰቅለኽ ዓለምን አድነኸዋል ሲሉ ነው፡፡
የእነዚኽ አርባዕቱ እንስሳ ፊታቸው በርካታ ምስጢራትን ሲያመለክቱ ገጸ ሰብእ በማቴዎስ፤ ገጸ አንበሳ በማርቆስ፤ ገጸ ላሕም በሉቃስ፤ ገጸ ንስር በዮሐንስ ተመስሏል፤ በሌላ ምስጢር የሰው ገጽ ያለው የጌታን ሰው የመኾንን ነገር፤ የላም መልክ ያለው በቀራንዮ ላይ ደሙን ማፍሰሱ፤ የአንበሳው መልክ ያለው የጌታችንን ትንሣኤ፤ የንስር መልክ ያለው የጌታን ዕርገት እንደሚያመለክቱ መተርጒማን ይተነትኑታል፤ዐምደ ሃይማኖት አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም እጅግ ምጡቅ በኾነው ዕውቀቱ ዕጓለ አንበሳ የተባለው የወልድ የባሕርይ አባቱን አብን በአንበሳ ይመስለዋል፤ ሥጋን ተውሕዶ ፍጹም ሰው የኾነው ወልድን የሰው መልክ ባለው መስሎ ገልጾታል፡፡ በአምሳለ ርግብ ወርዶ በወልድ ራስ ላይ ተቀምጦ የታየው መንፈስ ቅዱስን የንስር መልክ ባለው መስሎ አብራርቶ ጽፎታል፤ በቀንዱ የማይበራታ ላሕም ተብሎ የተመሰገነው የወልደ እግዚአብሔር ቅዱስ ሥጋው የሚፈትትባት፤ ክቡር ደሙ የሚቀዳባት በአራቱ ኪሩቤል አምሳል አራት መአዝን ያላት ቤተ ክርስቲያንን በገጸ ላሕም አምሳል ገልጦ አመስጥሮታል፡፡
ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድም በድጓው ላይ፡-
“አርባእቱ እንስሳ በእንቲኣነ ጸልዩ
ኢይልክፈነ ለእሳት ዋዕዩ
እንስሳ አርባዕቱ መናብርቲሁ ለዋሕድ
መተንብላን ለኲሉ ትውልድ”
(አራቱ እንስሳ የሲኦል እሳት ግለቱ እንዳይነካን ስለ እኛ ጸልዩ፤ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለውን አምላክ ዙፋኖቹ የኾኑ አራቱ እንስሳ ለትውልድ ኹሉ አማላጅ ናቸው) በማለት አንደተማፀነ እኛም የአምላካችንን ዙፋን የሚሸከሙ እነዚኽን ግሩማን መንፈሳውያን መላእክትን ከጌታችን ከአምላካችን ከክርስቶስ እንዲያማልዱን እንለምናለን፡፡
መጽሐፈ ሰዓታት ንባቡና ትርጓሜው ከሚለው መጽሐፌ የተወሰደ
የቤተክርስቲያን ትርጓሜ ምን ይላል ሊንኩን ይጫኑ።
ሐሙስ 23 ሜይ 2019
መቅድም
የሰንበት ትምህርት ቤት
እግዚአብሔር አምላክ የሰውንልጅ በአርያውና በአምሳሉከፈጠረ በኋላ ሰው ከፈጣሪውጋር በጥብቅ እንዲናገናኝ ልዩልዩ የአገልግሎት መንገዶችንአዘጋጀ። እያንዳንዱ በተሰጠውመክሊት ያተርፍና በጸጋውያገለግል ዘንድ በመጀመርያዕድሜው በፈቀደለት ሁሉመማርና ማገልገልይኖርበታል። እግዚአብሔርአምላክ መመለክ በአለበትአግባብ ለማምለክ እምነትያስፈልጋል፤ ከእምነትእንዳንወጣ ደግሞስለምናምነው ነገር በቂዕውቀት ሊኖረን ይገባል፤እምነትን፣ ተስፋና ፍቅርን ሰንቆእስከመጨረሻ ድረስ ለመጽናትመንፈሳዊ ዕውቀት መሠረታዊነው።
“ህዝቤ ዕውቀት በማጣትጠፍቷል” (ሆሴ 4፥6)የተባለው በእኛ ላይእንዳይፈጸም ዕድሜያችንበሚፈቅድልን ሁሉ ሃይማኖታዊዕውቀትን እንድንማር ቤተክርስቲያን በቅዱሳን ጸሎትበእግዚአብሔር መልካምፍቃድ ሰንበት ት/ቤትንአቋቋመች። ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ልጆቿ ጽድቅንይማሩ ዘንድ በሰንበት ት/ቤትአሰባስባ ቃለ እግዚአብሔርንአውቀው፣ ባሕርየእግዚአብሔርን ተረድተውእንዲያመልኩ፣ ሕጉንጠብቀው፣ በሃይማኖት፣በምግባርና በትሩፋት ፀንተውአምላካቸውን መስለውእንዲኖሩ የእርሱ የሆነችውንመንግስተ እግዚአብሔርንእንዲወርሱ በብሉይ ከአምላኳየተቀበለችውን ሕግጋተእግዚአብሔርን አስተምራበሐዲስ ኪዳንም በ40 እናበ80 ቀን እያጠመቀችለምዕመናን እንደ እድሜያቸውእና እንደ አዕምዕሮብስለታቸው ቃለእግዚአብሔርን ደከመኝ ሰለቸኝሳትል ታስተላልፋለች።በስብከት፣ በዝማሬ፣ በቅዳሴ፣በስዓታት፣ በማሕሌት የቅኔውንምሥጢር በትርጓሜእያስተማረች ምዕመናንንበእምነት አንፃ ለመንግስተሰማያት እያዘጋጀች ዛሬ ላይደርሳለች።
ከስሙ እንደምንረዳው ሰንበትትምህርት ቤት ማለት የጾታልዩነት ሳይደረግ የቤተክርስቲያን ተተኪ ትውልድወይም መንፈሳዊ ወጣቶችበዕለተ ሰንበት፣ በዓበይትበዓላትና አመቺ በሆነ ጊዜ ሁሉበአጥቢያ ቤተ ክርስቲያንእየተገኙ የቤተ ክርስቲያንንዶግማ፣ቅኖና፣ሥርዓትናትውፊት የሚማሩበት እናበእምነት፣በምግባርናበሃይማኖት ጸንተው ይኖሩዘንድ መንፈሳዊ ሕይወታቸውንየሚያጠነክሩበት ትምህርትቤት ነው:: መንፈሳዊ ወጣቶችየሚባሉት የኢትዮጵያኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ትምህርተሃይማኖት፣ ሥርዓትና ትውፊትበዕድሜ ክልላቸው የሚማሩየቤተ ክርስቲያን አባላት ናቸው(ቃለ ዓዋዲ ፲፱፻፺፩)።
በመጽሐፍ ቅዱስ ሰንበት ት/ቤት ተብሎ የተፃፈ ቀጥተኛየሆነ ስም ባይገኝም ዛሬ ላይበሰንበት ት/ቤት የሚተገበረውመንፈሳዊ አገልግሎት ማለትምልጆችን በቤተ እግዚአብሔርማስተማር በብሉይ ኪዳንዘመንም ይፈጸም እንደነበርመጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳናል።የሰንበት ት/ቤት ፅንሰ ሀሳብምከዚያ የመነጨ ነው። “እነዚህንቃሎች በልባችሁና በነፍሳችሁአኑሩ እነርሱንም ለምልክትበእጃችሁ ላይ እሠሯቸውበዐይኖቻችሁም መካከል እንደክታብ ይሁን ልጆቻችሁንምአስተምሯቸው በቤትህምስትቀመጥ በመንገድምስትሄድ ስትተኛም ስትነሣምአጫውቱአቸው” (ዘዳ11÷18-21 )በማለትእስራኤላውያን ልጆቻቸውንሕግጋተ እግዚአብሔርእንዲያስተምሯቸው ታዘዋል፡፡እነርሱም ይህን አምላካዊ ቃልተግባራዊ ለማድረግልጆቻቸውን ወደ ቤተእግዚአብሔር እየላኩ እናበቤታቸው ውስጥም ተግተውያስተምሩ ነበር።
በሐዲስ ኪዳንምመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስበመዋዕለ ሥጋዌ ልዩ ትኩረትከሰጣቸው ቁም ነገሮችመካከል ሕፃናት ወደ ቤተክርስቲያን ይመጡ ዘንድ ነበር።ልበ ንጹሐንን በሕጻናት መስሎያስተማረበት አንቀጽምበመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ተጽፎይገኛል። ይህም በዘመናችንላለችው ቤተ ክርስቲያንየሕፃናት፣ የወጣቶች እናየጎልማሶች ማስተማሪያለሆነችው ሰንበት ትምህርትቤት መነሻ የሆነ እናመሠረቱም መጽሐፍ ቅዱሳዊመሆኑን ያረጋግጥልናል (ማቴ18፥3፣ 21፥16፣ ማር 9፥37)፡፡
የሰንበት ትምህርት ቤትአመሠራረት በኢትዮጵያስንመለከት ዘመናዊ ትምህርትቤት እየተስፋፋ ሲመጣ ወጣቱትውልድ ከአምልኮተእግዚአብሔር እንዳይለይ፤በተለይ ለዘመናዊ ትምህርትአስተማሪነት በመጡእራሳቸውን ”ኢየሱሳውያን”ብለው በሚጠሩ የውጭመምህራን ከመጡበትዓለማዊ ትምህርት ባሻገርየኑፋቄ ትምህርትማሰራጨታቸው፣ በተቃራኒውደግሞ ወደ አብነት ትምህርትቤት የሚሄደው ወጣት ቁጥርበመቀነሱ ምክንያት በ20ኛውክፍለ ዘመን ወጣቱን ለመያዝመንፈሳዊ መርሐ ግብሮችናየማኅበራት እንቅስቃሴዎችተጀመሩ። እነዚህ የተጀመሩመርሐ ግብሮችና ማኅበራትየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶቤተ ክርስቲያንአስተምህሮዎቿ ሳይበረዙለትውልድ እንዲተላለፉ በተለይበሕጻናት እና በወጣቶች ላይትኩረት ሰጥው እንዲሠሩትልቁን ድርሻ ወስደዋል።
በዚህም መሠረት ሰንበትትምህርት ቤት በማቋቋምትውልድን በኦርቶዶክሳዊሃይማኖት የማነጽ፣ ዶግማን፣ቀኖናን እና ትውፊትንማስተማር ተጀመረ። በ1960ዓ.ም ይህን የሰንበት ትምህርትቤቶች እንቅስቃሴለማስተባበር እና ለማጠናከርይቻል ዘንድ በጠቅላይ ቤተክህነት በስብከተ ወንጌልናማስታወቂያ መምሪያ ሥርማእከላዊ ጽ/ቤት በዋናነትተቋቁሞ ስያሜውም የሰንበትት/ቤት መምህራን ጽሕፈት ቤትተብሎ ተሰይሟል፡፡ ይህአካሄድ እያደገ ሲመጣበ1965 ዓ.ም ራሱን ችሎ ወደወጣቶች ጉዳይ መምሪያነትእንዲያድግ ተደርጓል፡፡ ዛሬ ላይየሰንበት ትምህርት ቤትማደራጃ መምርያ የሚልሰንበት ትምህርት ቤቶችንየሚያደራጅና የሚመራበተቋም ደረጃ ትልቅ መምርያተቋቁሞ አገልግሎቱንእየፈጸመ ይገኛል።
የሰንበት ት/ቤት ጥቅሙናአስፈላጊነቱ የጎላ መሆኑበተግባር በመረጋገጡበ1970 ዓ.ም “ሰንበት ት/ቤት” በሚል ስያሜ ሕጋዊ ሆኖእንዲቀጥል እና በሁሉምአብያተ ክርስቲያናት ውስጥሰንበት ት/ቤቶች እንዲቋቋሙየተቋቋሙትም እንዲጠናከሩተሻሽሎ በወጣው ቃለ ዓዋዲእንዲጸድቅ ተደርጓል፡፡ የሰ/ት/ቤት አገልግሎትን የበለጠለማጠናከር ሰንበት ት/ቤቶችየሚመሩበትን መተዳደሪያደንብ አጽድቆ ሥራ ላይእንዲውል ያደረገ ሲሆን አሁንአስካለንበት ዘመን ድረስሰንበት ት/ቤቶች ይህንመመሪያ ከዋናው ቃለ ዐዋዲጋር በማስተባበርእየተመሩበትና ዘርፈ ብዙአገልግሎቶችን እየፈፀሙይገኛሉ፡፡
ይህን ወጣቱን ትውልድበዘመናዊነት ተፅዕኖ ውስጥወድቆ ከመንፈሳዊ ሕይወትእንዳይወጣ ልዩ ክትትልበማድረጉ ረገድ ኢትዮጵያ ብቻሳትሆን እኅት አብያተክርስቲያናትም ሰንበትትምህርት ቤትን አቋቁመውአገልግሎት መስጠት ከጀመሩብዙ ዓመታትን አስቆጥረዋል።በተለይ ግብፅና ሕንድበተደራጀ መልኩ እየሠሩበትይገኛሉ።
የሰንበት ትምህርት ቤትየተቋቋመበት ዋና ዓላማ
የሰንበት ትምህርት ቤትዓላማ፦
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንዶግማ፣ ቅኖና፣ እምነትናሥርዓት ተጠብቆሳይበረዝ ሳይከለስከትውልድ ወደ ትውልድእንዲተላለፍ ማድረግ
ማንኛውም የቤተክርስቲያኒቱ ተከታይ የሆነምእመን የሃይማኖቱንሥርዓት በውልእንዲያውቅና እንዲረዳማድረግ
ወጣቶች የቤተክርስቲያንን ሕግና ሥርዓትተምረው ለሀገርና ለወገንጠቃሚ፣ መልካምና በሥነምግባር የታነፁ ዜጎችእንዲሆኑ ማድረግ
በጉብዝናህ ወራትፈጣሪህን አስብ (መክ.፲፪፡፩) የሚለውን የአምላክተእዛዝ ወጣቶችእንዲፈጽሙ ማስቻል
እነዚህን ከላይ የተዘረዘሩትንአበይት ዓላማዎች ከግብለማድረስ ጠንካራ ሰንበትትምህርት ቤት ያስፈልጋል።ወጣቶችን በሰንበት ትምህርትቤት ለማሳደግ ከጠቅላይ ቤተክህነት እስከ አጥቢያ አብያተክርስቲያናት ሁሉም ባለ ድርሻአካላት የበኩላቸውን መወጣትበእጅጉ አስፈላጊ ነው።አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስለቅዱስ ጴጥሮስ ከሰጠውመመርያና ትዕዛዝ መካከልሕፃናትንና ወጣቶችንበሃይማኖት እያስተማረለመንግስተ ሰማያት ማብቃት